Tuesday, October 20, 2015

የጊዜ ጉዳይ
የጊዜ ከፍታ
የጊዜዉ ዝምታ
ጊዜ ስጡኝ ላንድ አፍታ
በአእምሮ በአሳብ ዝምታ
ስበላ ስጣጣ  ስለብስም ዝምታ
የሕይወት ጉዞ ከታምታታ
የኑሮ እንቆቅልሽ እስክፈታ፡፡
የአለቆች ብዛት  ጉዞ ሳይገታ
የእንቆቅልሽ ብዛት ሳፈታ
የቋጠሮ  ቁልፍ ምነዉ ጠፋ?
ይሁን እንጅ ይመጣል ከፍታ
ለጊዜዉ ዝምታ….
መከራ አይሆንም ጮርሶ ጌታ
ያበቃል የሰዉ ልጅ ዋይታ
የህይወት ዉል ቁልፍ መቀነቱ
አስረጅ ከጠፋ በሠዓቱ
የእንቆቅልሽ ዉል መብዛቱ
በዚያዉ አይቀርም ይነጋጋል ለሊቱ፡፡
አዎ የጊዜ ብዛት ዝምታ
የህይወት መጽሐፍ ብዛቱ
ገጽ ገለጻ ጊዜ ማጥፋቱ
ስክኖ ለጠበቀ አይቀርም ጊዜ መምጣቱ
የብቼኝነት ጣጣ ፍራቻ
የእንቆቅልሽ ብዛት ዛቻ
የህይወት ግጥም አጣን መምቻ
…ግን ይሁን የጊዜ  ባሮች
የነጻት አየር ናፋቆዎች
ጥንት ሲንፈጠር ነጸ ሰዎች
ዛሬ ግን የጊዜ ጉዳይ ሆኖ ባሮች፡፡
የጊዜ ከፍታ
የጊዜዉ ጉዳ ዝምታ…….

ኢያሱ ለገሠ

justice for Huamn

መዳዉ ሞልቶ ተርፎ የቁጥቋጦ ብዛት
እህሾህ ሆኖ ተገኘ ሲጠጉት
የህመም ብዛት የሰዉ ዉጋት
ጥላ ላይሆን ሲጠጉት…..!
ይሆናሉ ብየ ተጠጋሁት ጥላ
ጸሔም በረታ አጠሁኝ መላ
ሰዉ መሆን ቀሬ ወይ  ከሌላ?
ሲያጨበጭቡ  አጭብጭቤ ሰዉ መስሎኝ አቅፌ
ማር ጣፈጭ ሲል በአፌ…..
ሰዉ ሆነ እኮ ለስብራቴ
ወገሻ አጣሁ ለህመም  በቤተ፡
ሰዉ ጥሩ ነዉ አብሮ ሲበላ
በችግር ጊዜ ጠፋ የሰዉ ዱካ ጥላ፡፡
ይመሰልሉኘ  ነበር  የጀምበር ጥላ
ሰዉ የፈጠረ አማልክ ካላለ መላ
የተስፋ ዳቦ እኔ አልበላላ
አልሆን ብሎኝ ዉሽትና ድሌላ፡፡
በሰዉ ሀገር መቼ ልደላ
ብቼኝነት አንጀትን በላ
መጫን ማዉርድ  የእኔ ሥራ
ይለኝ ጀመር ጋዝ 
ጋዝ ቃሪ ቃሪ
ከወገን ተነጥሎ መኖር
የክብር ሸማ የለም በሰዉ ሀገር
የጉዞ ጅምር የሕይወት ከፍታ
ህይወት ጎዞ ከዝቅታ፡፡
የጸሐይ  ጅንበር ናቸዉ ሲታዩ
ዓይናቸዉ  ጥቁር ሰዉ አያዩ
የዘረኝነት ማጥ ሸጡ
ጥቁሮች በአንድነት ነጻ ዉጡ
ዳኝነት አጣ ጥቁር ቆዳ
መሆኑ አልቀረም የትውልድ እዳ
እንቆም የዘር ሀረግ ፍዳ
ብቼኝነት  እኮ  ነዉ መዘዙ
ለመንቀል ይህንን ሰንኮ መርዙ
በሰዉ ሀገር ሰዉን  በግፍ የሚገዙ
የጣላ ወይም የጋንጃ ማህበር ብደራጅ
አንድ መሆን አይችልም መቼም  አይበጅ
በአሳብ ልዩነት ሲፋጅ
የብቼኝነት ህመም ዘልቆ ገባ ቁሲል
ሰዉ አጣሁ ልብ የሚል
የአዳም ዘር  ጠፋ ዉሉ
ለህመም ለቁሲል መላ በሉ
Dr Eyasun    

2013
የዓረብ ዓለም ንግስት
በሕይወት ሳለች የሐዘን ልብስ ለብሳ
የመከራ እሳት በላይዋ አንግሳ ፣፣
ተጨንቃ  ተጠባ ለቤተሰብ አባሳ
የጽናት ተምሳለት የቤተሰብ መሰሶ
ጠራ ግድግዳ …..የሕይወት ዉሎ
አልደረቀም የእንባ
ለመከራ እንጃራ ሲትል ባባ
አረብ መቺ ጅሮ አለዉ ልስማ
በአረብ ምድር ሲትል ቀና ደፍ
የኒ ማኛ ብሎ አንገት ልያስደፍ
የዓብ ዓለም ንገስት መቼ ልትሰማ
ጥድፍያ ተያይዘዋል  ለማምለጥ ከጨለማ
የዓረብ ንግስቶች ቀንደርሶ ይኖራሉ በክብር ማማ
ነጻ  ይወጣሉ  በግፍ ከጨለማ፤፤
የሕወይት ዘመን እንጀራ ሲታሰፋ
ከመቼዉ አበዶ ይሆን የስድብ ጥሩባ የሚነፋ?
የዓረብ ዓለም ልእልት  የቤተሰብ የመኖር ተስፋ
ሐዘኑዋን አትናገር  በግፍ ምድር ብትከፍ፡፡
ያንተ ምላስ ምነዉ ከረፋ…….
የሀገር ሀግት ናቸዉ የዉበት እንቁ
ገረድ አለመሆንዋን  ሕዝብ እወቁ
ሀገር ገዳይ መረዝ ምላሱ
ትውልድ ሲራገም በምድር  የለም ወይ ንጉሱ?
ሠርቶ መኖር  ከመሰለዉ ወርደት
ሀገር እና ሕዝብ ከመረገመ ይባለዉ አቶን እሳት፡፡
ካልወደዱ በዓረብ ምድር አይደፈር ሕልቁ
ስፈልጉ  አረብ በሳጃ የምሞሽልቁ
ለእንጀራ ሲሉ የተገፉ  ነጻነታቸዉን የሚወዱ
አትኩይ ባይነት ልብስ ልብሶ ሥራቸዉን የሚሠሩ
ጊዙዉ ሆኖ ማንንም የማይፈሩ የተወዲሮስ ልጆች ናቸዉ፡፡
ለአሠር   መልስ እሰጠች ካልወወክ አሁኑኑ አሳፈረኝ ባዮች
የሞራል የመንፈስ ጅግኖች አንተ ግን ስም ሰጠሃቸዉ…
ጥቁር መጋረጃ ልብሶዉ ሠራተኞ ናቸዉ፡፡
ሲቀናቸዉ ማዳሜን በጡጫ የሚያትወለዉሉ እኛ ምስክር  ነን
አልሞት ባይ ተጋዳይ
ዝምታን የመወያዉ ለገዳይ›….
አለቅላቅነት ካባ አዉልቆ  ጥቃትን የማይወዱ
ለአንድ ደቅቃ  ለዓረብ የማይሰግዱ
የጀግና ትውልድ ምሳለ… ቅኝ ግዛት አላቅም ባይዮች
የዓረብ ዓለም ሴት  የእግር እሳት ናቸዉ ለአስመሳዮች፡፡
በል ተፋርድ.. የሀገር  ሴት ጥለህ በቆሸሻ
ትሳደባለህ  እንደ ስትሻ …
ከወደዱህ እስከ ሞት ይገዙልሃል ዘር ቀለም ሳይመርጡ
ከጠለሁ ደግሞ ይጨምሩብሃል እሳት ረመጡ
የዓረብ ዓለም ሴት የሀገር ጅግና ናት  በእግር አትርገጡ ፡፡
ክቡር ናት እና አትድፈሩ ክብVን
የመከራን እሳት ረግጣ ልጅ ታስተማረች ቀና ሳትል ጎንበስ ብላ፡፡
Dr EYASU LEGESSE
አረብ ሀገር ያለች የቤተሰብ የጅርባ አጥንት
የቤተስብ መመኪያ  የወገን መኩሪያ
እጆች ትስነዝርያለች ጀንባር ጠልቃ ቢዚያ
አንቺ ሞተሸ ለሞት ትንሳኤ ሆነሽ
ተብረሽ እንዳልተራብሽ ተገፍተሸ እንዳልተገፋሽ
የአረቦች የቁጣ አምርጩሜ ስገርፍሽ
ግፈኛዉ የናስ ያለ ስም  ስም ሰጠሸ፡፡
ይሁን ግድ የለም ባንቺ ሞት ቤተሰብ በሕይወት ከኖረ
ክብር ዝና ብቀር
ታረክሽ ሕያዉና ነዉ በርቺ እህቴ…
የጉስቁልና ቀንብር ካንቺ ተሰብሮ
ይብራ የነጻነትሽ  ይችቦ፡፡
ሀገሩን ያልማ ሁሉም ተባብሮ
የናስ ማኛ የክፍለ ዘመኑ ዜሮ
የአረብ ሀገር ልጆች ተነሱ ተባባሮ
መኖር እንዲያበቃ አካልን ገብሮ
ፈራጅ አልነበርም ሲንሞት ከፎቅ ተወርዉሮ
ቀና ብለሽትሄጃል  የዉርት ቀንበር ተሰብሮ፡፡
ሁሉም ለሥራ ይትጋ ለመስራት ተባብሮ፡፡