Tuesday, December 1, 2015

ከሕግና ሥርዓት ዉጭ የሆነ የፖሊስ አሠራር በዓለማቀፍ በሕግ ይዘት የለም፡፡ የኩዌት ፖሊስ የሀገርቱን ሕግ ጥሶ ታስርዎችን ወደ ኢትዮጵያ ኤምባስ ማቆያ ለቀቀለቸዉ የሚለዉ የእግር እሳት ነዉ የሚሆነዉ፡፡ ምክንያቱም በኤምባስዉ አአስተዳደር ሥር ከሆኑ ተመሳሳይ የሆነ ቪዲዮ አዘጃቶ እያለቀሱ ሳይሆኑ እየሳቁ ሊነግሩን ይገባል፡፡ ይህ የፈጠራ አዳባባይ ትንግር ማደናገርያ ዜና ለቤታቹና ለጆሮአችሁ እንዲህም ለሕሊናቸዉ አድምጡት፡፡ ከአመታት በዘለቀ ሁነታ ሥርዓት አልበኝነት ወይም ሕግ ወጥ እንቅስቃሴ ላይ ያገኘዉ ማንኘዉም ግለስብ ፖሊስ በሠዓትት ልዩነት ታምራዊ እርምጃ ወሰደ ፈታቸዉ ስትሉ ለጆሮ ይቀፋል፡፡ ህጌ ወጦች ከለቀቀ ሕግ ወጡ ፖሊስ ነዉ ማለት ነዉ፡፡ የኩዌት ፖሊሶችን ሕግና ሥርዓት ማስተማር ይጠበቅብናል ማለት ነዉ፡፡ መኖርያ ፈቃድ ሳይኖራዉ መኖር ወንጅል ነዉ፡፡ ያንን ሕግ ጥሶ ሕገወጦቹ የሚቆበት መኖር ፈቃድ ወረቀት ሳይሰጣቸዉ እንዴት በምን ታምረ ተለቀቁ? የወንጅል ምርመራ ሕግ አልተማሩም? እንዲህ ዓይነት ሕግ የለም?ዋስናት የሚለዉ ብህል አይሠራም፡፡ ከመጀመሪም መኖር ፈቃድ የጨረሰ ሰዉ መቆየት የሚለቸለው ፈቃዱን ማስረዘም ሲችል ነዉ፡፡ ለተአምታነት ያ ያለቅሱ የነበሩ ሴቶች በመጠለያ መኖራቸዉን የሚያሳይ የምስል ዊዲዮ ለምን አልተለቀቀም? ፖሊስ ከህግ አሠራር ዉጭ ወደ ማንም መጠለያ አይመልስም፡፡ አየር መንገድ ወደ በበራ በር ወደ ዉስጠኛዉ ክፍል በታሸገ መክና ወስዶ ሲያራግፍ አየር መንግድ በሚሠራበት ወቅት ተመልከቸዋለለሁ፡፡ ይህ ብቻ ሳይሆን በከፍተኛ ወንጅል ምክንያት ተፈርዶበት ወይም ከሀገር እንድወጣ ፍርድ ቤቱ ሲወስን ከሁለቱ እጆች ሰንሰለት ተደርጎ ሕዝብ እንዳያየዉ ነጭ ጨርቅ ወይም የሆነ ጨርቅ በሁለቱም እጆች ጣል አደርጎ በሰላማዊ መንገድ ሕዝብ ሳይደናገር ከሀገር ያስናብታሉ፡፡ ኢትዮ በኩዌት እስረኞች በምን ታምራት በሠዓት ወደ አሻራ ክፍል እንዳመራቹ ወደ ማቆያ እንደ ወሰዳቹ ለማመን ያስቸግራል፡፡ ሕጌ ወጥ ሰዉ ወንጅል ሳይመራምር ብምንም ታምሪ ወደትም አይልክም፡፡ በእርግጥ እስር ቤቱ ልትጎበኙ ትችላልሁ፡፡ የመብት ጥያቄ መጠየቅ አላቹ፡፡ ማንም እስረኛ ማንቀሳቀስ ከቶ አትችሉም፡፡ በትክክል የማደረግ መብት የሚኖራቹሁ ኢትዮጵያዊ መሆኑን ፖስፖርት የሌለዉ ሆኖ ሲገኝ የይለፍ ወረቀት ከማቅረብ ዉጭ የቱ ነዉ የእናተ መብት? አሁን ፕርዝነር ብረክ ፍሊም ይመስላል፡፡መላ ኢትዮጵያዊ ለማሳስት መኩራ ራሱ ጸያፍ ነዉ፡፡ ከመጀመሪያዉም ለኢትዮጵዉያን እና ለኢትዮጵዊነት የሚገዳች የአስተዳደር ሰዎ አለመሆናቹን ብዙ ማሳያ አለ፡፡ ነገር ግን በአንድ ቀን ዉስጥ ይህ ታምራት አድርገናል የሚትሉት እጅግ አሳማኝ ሰነድ አይደለም፡፡ አንድ ቀን የጉዞ ሰነድ አዘጋጅተናል የሚል ታማንነት ይጎላል፡፡ለምን ብቢል የንን ሁሉ ለማድረግ 30 ቀን ያላነሰ ጊዜ ይወስዳል፡፡ በእናተ በጨለማ ትኖሩ ይሆናል፡፡በዉሸት ጊርዶሽ በመጋረጃ ዉስጥ ከዉስጥ ወደ ዉጭ ማየት ላትችሉ ችላል፡፡ከዉጭ ሆኖ ለሚመለከታችሁ በበርሃን ላይ ናቸሁ፡፡ በሠዓታት ዉስጥ ይህንን ታዓምራት ለመፈጠር ከቻላሁ ከሆነ ኩዌት ኩታዉያን ሳይሆን የመከያስተዳዱሩት የኢትዮ ኤምባስ ነዉ ማለት ነዉ? ፖለስ የማጣራት ሥራ አይሰራም ወንጅ ያለበትና ወንጅል የሌለበት ሰዉ አያጣም? እስከ መቼ ትድረስ ትንግርት ድራማ እኔ ብቻ ሳልሆን በጽ/ቤት ተጽፎ የወጣ ደብዳቤ ሁሉም ሰዉ እንደሚያነብ ማሰብ ተገቢ ነዉ፡፡ በሥነ ሥርዓት የታሠረ እስረኛ ከዚያዉ እስር ቤት ምርምራ አልቆ ከወንጅል ነጻ መሆኑ ሲታወቅ ከሀገር ይወጣል፡፡ የወንጅል ሒሳብ ካለበት በመደበኛ ፍርድ ቤት ይዳኛል፡፡ሌላዉ በማቆያ ዉስጥ ናቸዉ የሚል ለጆሮ እጅግ ይቀፋል፡፡አረብ ሕግ ቀርጾ የወንልጅ ከሕግ ከብረት የበረታ ነዉ፡፡ የወንጅል ምርመራ ሳያደረግ ወደ ማቆያ አመጣናቸዉ የሚል ጭልጥ ያለ ክህደት ሸፍጥ የተሞለበት ነዉ፡፡ፖሊስ ወንጅል ሳይመርም ኤምባስዉን አክብሮ ወደ ኤምባስ ማቆያ መልሶታል የሚለዉ ደብዳቤ ያሳፋራል፡፡ልብ እንበል አንድ ሕጌ ወጥ ሰዉ ከህግ ዉጭ ሲቀሳስ ከተያዜ የህግ ጥሰት ፈጸሞ ሲገኝ በፖሊስ እጅ ቆያል፡፡ልያሠራዉ ያመጣዉ አካል ይጣራል የወንልጅ ተግባር መኖር አለመኖር ይመረመራል፡፡አሠራዉ እንድፈታ ፈቃድ ከሰጠ ይቀጥላል፡፡ከሀገር እንዲወጣለት ሲያመለክት ትኬት አዘጃቶ ከ ወር እስከ 2 ወር ጊዜ ገደብ ወደ ሀገር ይመለሳል፡፡ አንዳንዱ ደግም በጭከነ የተሞላ አረብ ከሀገር እንዳይወጣ የፈረም እንደሆነ ያ መትፎ ቅጣት ነዉ ኤወጣም፡፡ መኖርያ ፈቃድ ያለ ሥራ ያለ ዘግነት እየተቀጣ እንድኖር ከፈረመ ይህ አይነቱ ቅጣት እጅግ መጥፎ ነዉ፡፡ በዚህ ዓይነት የተቀጣ አንድ አሜሪካዊ አለ፡፡ ሌሎች ዜጎች ይኖራሉ፡፡ በስም ደረጃ ባላዉቅም ከ15 ዓመት የተቀጡ በአፍ ደረጃ ይነገራል፡፡ ግን ማን ይሁን ማን መረጃ ለማግኘት አለመቻለ ነዉ፡፡ የእኛ የኤምባስ ምሁራን የህግ ሊቆች ይህንን ግዙ የሆነ ሰነድ ፈስ ቡክ ገጽ ሲለትፉ ምስጋና ከመሻት አንጽር ከሆነ ተገቢ የሆነ አሠራር ከሕግ ያፈነገጠ ድርግት እላለሁ፡፡ ምክንያቱም እግራቸዉ ፈጥኖ የማይራመድ እጃቹ ከሰጭነት ይልቅ ተቀባይነት መተሳስብና ማቻቻል ለመሰበክ ይልቅ መከፋፈል የአማራ ልማት የትግራይ ልማት የኦሮሞ ልማት የሙስልም ማህባር የክስቲያን በሴል እያደረጃ እየሰነጣጠቁ የተጠመዱ ከመሆኑም በላይ ፈጥኖ ሮጦ የሚደርሱ ለቅንነትና ለፍትህ የቆሙትን ከፍፍሎ በታትኖ አደገኛ አደረጃጃት እና አስላላፍ አስልፎ ግዙፍ የሆነ በጠራራ ጸሐይ የእስረኞችን የማስለቀቅ ሠራ አሉን… ካሉ በርካቶች ፍርድ በማጣት መራር ለቅሶ የሚያለቅሱ ማን በነገራቸዉ የቤተሰብ ልብ ለመስብር የማይፈልጉ ግን ሲብራቱ ተሸክሞ አሉ፡፡ ከሕግና ከሞራል አንጻር ሲንመለከት ከእኔዚህ ሴቶች ማን አመጣቸዉ የሚለዉ ጥያቄ አብሮ መታየት አለበት፡፡ የኩዌት ፖሊስ ወይም የትኛዉም ሀገር ፖሊስ ወንጅል ሳይመራምር የማንም እስረኛ ማቆያ አይመልስም፡፡ ይህንን ያንንም አልሠራችሁም ብሎ የሚጠይቃችሁን ማህበረስብ መልስ ለመስጠት ከሆነ እጅግ ሲህተት ያለበት ደብዳቤ ነዉ፡፡ በሰማይ ሆኖ የሚያዉን አምላክንም መፍራት ጥሩ ነዉ፡፡ ኩዌት ዉስጥ የአእምሮ እብደት የለሌባቸዉን እብድ ተብሎ በእብዶች ሆስፕታል ያሉ ሴቶች አሉ፡፡ እስፕሰሮቻቸዉ እብድ ናቸዉ ብሎ ፈርሞ ያስገባሉ ያ ሰዉ መልሶ ካልፈረመ ማንም አያወጣም፡፡ እኔ መከራከር መብት የለኝም፡፡ ለጥብቅና አልችልም፡፡ ሕጉ አይፈቅድም፡፡ ይንን የመሰለ ታላቅ ችግር ኤምባስ ብቻ ይፈታል፡፡ጆሮአቸዉ ሰማል ብየ ለሚያስባቸዉ በተጋጋም ከመናገር ከመጸፍ ዉጭ ሌላ በአረብ ሀገር ከቶ አይቻልም፡፡ ማን ማነህ ይሉሃል፡፡ የኤምባስዉ እምነታና አስተሳስብ የንግድ ሲስትም የፖሊቲካ ትቅሞች ላይ ማተኮር ገንዘብ እንዴት መሰብስብ እያንዳንቸዉ ጥቅማቸዉን ማስከበር እንዳለባቸዉ የሚሠሩ የተለያዩ ገጸ ባህርይ ይጫወታሉ፡፡ማንኛዉም ገንዘብ ምንች ልመጣ የሚችለዉ ዜጎች በድህነነት ሲኖሩ ነዉ፡፡ ከኩዌት ወደ ኢትዮጵያ ሚገባ ቱሪት የለም፡፡ከኩዌት ወደ ኢትዮ የሚፈስ የገንዘብ ምንጭ እዚህና ሌሎችአልቃሾ ዜጎች ናቸዉ፡፡የእኛ ደህንነት በአግባቡ ካልጠበቀ ገንበዙን ከማን ልሰበስብ ነዉ? የሆቴል ሥራ የተጠመዱ ግለሰቦች በሆተላቸዉ አረብ እንድመገብ ሳይሆን ድህነንቱ ያልጠጠበቀ ሚስክን ኢትዮጵያዊ እንድመገብ ታሰቦ ነዉ፡፡ ኢትዮጵያዊ ሲደልና ሲረገጥ ልቆም የማይፈልግ ነጋድ በሕዝበ ልነግድ ከቶ ሞራል የለዉም፡፡ በኩዌት ዉስጥ ያለ ኢትዮጵዊ በኤምባስ አስተዳደር በበልሹ አስተዳደርና ጎጠንነት ምክንያት ዋስትና የለዉም፡፡ የብዙ ሰዉ ሕይወት ተናግቶአል፡፡ የዉጭ ጉዳይ ሚኒሰተር በኩዌት ለብሎች ከወሮበሎች ጋር ተደራደሮ መሄዱ የማይካድ ጉዳይ ነዉ፡፡ የሁለት ሀገር ግንኙት የሰመረ ማደረግ ያልቻሉ በቅራነ ዉስጥ ያሉ ሀገሮች ናቸዉ፡፡እንደ ባግለድሽ ዜጎች አንድ በአንድ እየለቀሙ ኢትዮጵያዉን በማዉጣት ላይ ናቸዉ፡፡ ለብሔራዊ ጥቅም ሳይሆኑ ጥቅማቸዉን አስጠብቆ መሄድ ላይ የተጠመዱ ናቸዉ፡፡ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም የሚለዉ አገላለጽ የተሳሳተ ነዉ፡፡ ግላዊ ጥቅም፡፡ ጎሳዊ ብልጽግና ብሔራዊ ጥፋት ላይ ያተኮረ አስተዳደር ነዉ፡፡ ከተጠያቅደነት ለመዳን ሲባል ያልጠሠራ ሥራ ተሠራ ብሎ ማህተም ብቻ በመኖርና ለድብዳቤ ቀንና ቁጥር እየለጠፍ ደብዳቤ ማዉጣት ከታሪክ ተጠያቅነት ነጻ አያደርግም፡፡ እስረኞቸቹ በአዲስ ዊደዲዮ ልያረጋግጡልን ይገባል፡፡ ማቆያ ላይ ከሆነ ነጻ ናቸዉ ምን ያስፈራቸዋል የሚለዉን ሰዉ አያስብም ዓይነት ከሆነ ጫወታዉ ከመጋረጃ በሲቲያ ነዉ፡፡ መልካም የዉሸት ጊዜ፡፡

No comments:

Post a Comment